የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሚመለሱበት ቀን ታውቋል ?

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሳቢያ ከትምህርት ተቋማት የወጡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወደትምህርት / ወደሚማሩበት ተቋም / የሚመለሱበት ቀን እስካሁን ድረስ በመንግስት ተወስኖ አልተገለፀም።

በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች 'የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሚመለሱበት ቀን ታወቀ' ፣ 'የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎችን የምርቃት ቀናቸው ተወሰነ' በሚል የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰተኛ ነው።

በቅርቡ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎች እስኪጠሩ ድረስ ከቫይረሱ ራሳቸውን በመከላከል ባሉበት ሆነው ንባባቸውን እንዲቀጥሉና በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ እንዲሁም በአከባቢያቸው ያሉ ወገኖችን እንዲያስተምሩ መልዕክት ማስተላለፉ ይዘነጋም።

@tikvahethiopiaBot @tsegabwolde