የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳይ!

የኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ወረርሽኝ የሚገታበት ጊዜ ባለመታወቁ የሚጀምራቸውን ትምህርቶች ለመለየት መቸገሩን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁን አሃዱ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል፡፡

በቫይረሱ ምክንያት በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይሰጡ የነበሩ መደበኛ ትምህርቶች ተቋርጠው የተወሰኑትን በመለየት በበይነ መረብ አማካኝነት የመማመር ማስተማሩ ሂደት መቀጠሉ ይታወቃል፡፡

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ለመደበኛ ተማሪዎች በበይነ መረብ አማካኝነት እየሰጡት ያለውን ትምህርት በክረምቱ እንደማይቀጥሉ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር ባደረጓቸው ውይይቶች ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተሰምቷል።

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ግን በመደበኛው ትምህርት የተጀመረው ሙከራ ተስፋ ሰጪ ነው ብሏል፡፡

የኮሮና ቫይረስ ወረርሸኝ መቼ እንደሚቆም አለመታወቁ መደበኛውን ወይስ ደግሞ የክረምቱንና የርቀቱን ለመጀመር ቁርጥ ውሳኔ ማሳለፍ አልተቻለም - #AhaduRadio

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia