#DrTedrosAdhanom

"የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እየተባባሰ ነው " - WHO

ምንም እንኳን የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭት በአውሮፓ እየቀነሰ ቢሆንም በዓለም አቀፍ ደረጃ ግን እየተባባሰ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም አስታወቁ።

ዳይሬክተሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ ባለፉት 10 ቀናት ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ገልፀዋል።

ትናንት ከተመዘገበው ከ136,000 በላይ ኬዝ 75 በመቶ የሚሆነው የተገኘው በአስር (10) አገራት ሲሆን አብዛኞቹ አሜሪካ እና ደቡብ እስያ ውስጥ የተገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ በበርካታ አገራት የታየው አዎንታዊ ለውጥ አበረታች እንደሆነ ዳይሬክተሩ ዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም አክለዋል።

"አሁን ላይ የእነዚህ አገራት ትልቁ ችግር #ግድየለሽነት ነው። ምን ያህል ሕዝብ ለቫይረሱ እንደተጋለጠ የሚያሳዩ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት አሁንም በዓለም ላይ ያለ አብዛኛው ሰው ለበሽታው ተጋላጭ እንደሆነ ያሳያል" ሲሉም አስጠንቅቀዋል።

#BBC #GoaChronicle
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia