TIKVAH-ETHIOPIA
#DrLiaTadesse በኢትዮጵያ ተጨማሪ 2 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 912 ላቦራቶሪ ምርመራ 2 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 133 ደርሷል። የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦ ታማሚ 1 - የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ #ከኬንያ የተመለሰና #በሞያሌ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ። ታማሚ 2…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በደቡብ ክልል ሀላባ ዞን በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] መያዙ ስለተረጋገጠው የ25 ዓመት ወጣት ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አጥናው ካውዛ ፦

- በደቡብ ክልል በኮሮና ቫይረስ መያዙ የተረጋገጠው ወጣት በዛሬው ዕለት በጤና ሚኒስቴር መገለጫ የተገለፀው ሁለተኛው ታማሚ ነው።

- ወደ ሱማሌ ክልል ናሙና ተልኮ ምርመራ ተደርጎ የናሙናው ውጤት ሳይጠናቀቅ ሰዎቹ ከሞያሌ ወደ ደቡብ ክልል እንዲንቀሳቀሱ ነው የተደረገው።

- ቫይረሱ እንዳለበት የተረጋገጠው የ25 ዓመት ወጣት የከምባታ ጠምባሮ ዞን ነዋሪ ነው፤ ከኬንያ ነው የተመለሰው፤ ወጣቱ ትላንት ለሊት ወደ 11:30 #ሀዋሳ ገብቶ ነበር። 11:45 በሌላ መኪና ወደ ሀላባ ሄዷል፤ በኃላም በጤና ሚኒስቴር ሪፖርት ክትትል ተደርጎበት #ሀላባ ላይ ተይዟል።

- ከወጣቱ ጋር ወደ ሀላባ በአንድ መኪና የሄዱ ሰዎች በሙሉ ተለይተው ተይዘዋል። ሌሎች ከእሱ ጋር አብረውት ከሞያሌ የመጡም የተወሰኑ ሰዎች ተለይተው ተይዘዋል። አሁንም ቀሪ የማጣራት ስራዎች እየተሰሩ ነው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot