አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች፦

- አርጀንቲና ግዙፉን የኢግዚቢሽን ማዕከል ወደ ኮቪድ-19 የህክምና ማዕከል ቀይራለች። እስከ 2ሺህ 5መቶ የሚጠጉ የኮቪድ 19 ታማሚዎችን ለማከም እንዲውልና ማዕከሉ በሆስፒታሎች የሚኖረውን ጫና ለማገዝ እንደሚረዳ ተገልጿል #VOA

- በዩናይትድ ኪንግደም ባለፉት 24 ሰዓት 888 ሰዎች ሞተዋል። ቁጥሩ ባለፉት 7 ቀናት ከተመዘገበው ከፍተኛው ነው። በሌላ በኩል 5,526 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቅላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 114,217 ደርሷል።

- በጃፓን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 10,000 ደርሷል።

- በአውሮፓ ብቻ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1,000,000 ደርሷል።

- ደቡብ ኮሪያ ባለፉት 24 ሰዓት 18 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ሪፖርት አድርጋለች። ዘጠኙ ከውጭ የገቡ ናቸው። በደቡብ ኮሪያ ከFebruary በኃላ የተመዘገበ ዝቅተኛው ኬዝ ነው።

- በቻይና 27 ተጨማሪ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። አስራ ሰባቱ (17) ከውጭ ሀገር የገቡ ናቸው።

- በጣልያን በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች እንዲሁም የሟቾች ቁጥር መቀነስ አሳይቷል። ባለፉት 24 ሰዓት 482 ሰዎች ሲሞቱ 3,491 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

- በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት 585 ሞተዋል።

- ጅስቲን ትሩዶ የካናዳ እና የአሜሪካ ድንበር ተዘግቶ እንደሚቆይ ተናግረዋል። ድንበሩ ተዘግቶ እንዲቆይ ሁለቱም ሀገራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውም ተሰምቷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia