#JimmaUniversity

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት ሶስቱም ፋካሊቲዎች እና በሆስፒታሉ በማገልገል ላይ ያሉ የአካዳሚክም ሆነ የሆስፒታል ሰራተኞች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት በሙሉ አቅማቸው እንዲሳተፉ ተወሰነ።

ሁሉም የኢንስቲትዩቱ ሰራተኞች የኢንስቲትዩቱ አመራር እና የኮሮና ቫይረስ መከላከል ግብረ ኃይል በሚመድባቸው የስራ ቦታ ላይ ይህ ችግር እስኪያልፍ እንዲሰሩ ተወስኗል። ሁሉም ሰራተኛ ለሚደረግለት ጥሪ አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ስለሚጠበቅበት እንዲዘጋጅ መልዕክት ተላልፏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia