አጫጭር አለም አቀፍ መረጃዎች፦

- ፊልፒንስ ተጨማሪ የ73 ሰዎችን ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች። አጠቅላይ 360 ሰዎችም በሀገሪቱ በቫይረሱ መጠቃታቸው ተነግሯል። በሀገሪቱ በ24 ሰዓት ውስጥ 6 ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 25 ደርሷል።

- ቻይና በሀገሯ የሚዛመትን አዲስ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ መቆጣጠር ብትችልም ከውጭ የሚገቡ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ዛሬም መጨመር አሳይቷል።

- በኮሮና ቫይረስ 2 ሰዎች የሞቱባት፣ እንዲሁም 432 ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁባት ሲንጋፖር የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ማንኛውም ግለሰብ ለአጭር ጊዜ ጉብኝት [በትራንዚትም ቢሆን] እንዳይመጣብኝ ብላለች።

- የሮማኒያ መንግስት በሀገሪቱ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ሞት መመዝገቡን አሳውቋል። ሟቹ እድሜያቸው 67 እንደሆነና የካንሰር ህመምተኛም እንደነበሩ ተገልጿል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia