#ETHIOPIA

- በአሁኑ ሰአት ከቻይና በተጨማሪ እንደ ጣሊያን፣ ኢራን፣ ደቡብ ኮሪያ እና የመሳሰሰሉ ሀገራት የሚመጡ መንገደኞች ላይ ተጨማሪ ክትትሎች እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።

- ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሀገራት የሚመጡ መንገደኞችን ቅፅ በማስሞላት እና አድራሻቸውን በመያዝ በስልክ ተጨማሪ ክትትሎች እየተደረገላቸው መሆኑ ተገልጿል።

- እስካሁን ከተለያዩ ሀገራት የመጡ 1 ሺህ 20 መንገደኞች ተጨማሪ ክትትል የተደረገላቸው ሲሆን፥ 1 ሺህ 93 መንገደኞች ደግሞ በስልክ ከትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

- ጤና ሚኒስቴር ቫይረሱ ቢከሰትም በፈጥነት መቆጣጠር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ ሲሆን፥ የሆስፒታል ዝግጅት፣ የግብአት እና የባለሙያዎች ዝግጅትም በስፋት እየተሰራበት ነው።

- የኮሮና ቫይረስ ጉንፋን መሰል ምልክቶችን የሚያሳይ እና የመተንፈሻ አካላትን የሚያጠቃ ቫይረስ ስለሆነ ህብረተሰቡ ጥንቃቄዎችን ማድረግ ላይ መዘናጋት አንደሌለበት ማሰስቢያ ተሰጥቷል።

- ኮሮና ቫይረስን [COVID-19] በሚመለከት በማህበራዊ ሚዲያዎች በሚሰራጩ መረጃዎች ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ መረጃዎች ትክክለኛ መሆናቸውን በማረጋገጥም የበኩሉን ደርሻ እንዲወጣ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

- መላው ህብረተሰብ ኮሮና ቫይረስን [COVID-19] ቀድሞ ለመከላከል የግል ንፅህናን መጠበቅ እና ንክኪዎችን መቀነስ ላይ ትኩረት ማደረግ አለበት ተብሏል።

- ህብረተሰቡ ከኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ጋር በተያያዘ የሚያጠራጥሩ ነገሮችን ሲመለከት ሆነ መረጃዎችን እና እርዳታዎችን ለማግኘት ወደ 8335 መደወል እንዳለበት መልዕክት ተላልፏል።

#DrLiaTadesse #ኤፍቢሲ #ጤናሚኒስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia