#EthiopianPressAgency

በኢትዮጵያ ፕሬስ ደርጅት ዛሬ መጋቢት 1,2012 ቀትር 5: 50 ገደማ የተሰራጨው ፎቶ በስህተት አንደሆነ እና ጥፋትም እንደሆነ ምስሉን የተጠቀመው ጋዜጠኛ ድልነሳው ምንውይለት የተናገረ ሲሆን ይቅርታም እንደጠየቀ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ጌትነት ታደሰ ለwww.fidelpost.com ተናግረዋል።

”ነገሩ እንደተከሰተ ወዲያው ነው ይቅርታ የጠየቀው። አጥፍቻለው። የሰራሁት ነገር ስህተት ነው።” በማለት ጋዜጠኛው ለድርጅቱ እንደተናገረ አቶ ጌትነት ተናግረዋል።

የተቀነባበረው ፎቶ እንዴት ጋዜጠኛው ኮምፒውተር ላይ ሊገኝ ቻለ? ተብለው የተጠየቁት አቶ ጌትነት ”ልጁ ስህተቱን አምኖ ይቅርታ ጠይቋል። እኛም እንደ አስተዳደር ከስራ አግደነዋል። ሌላውን ጉዳይ ፓሊስ እያጣራ ስለሆነ ከዚህ በላይ ምንም ልል አልችልም ” ብለዋል።

www.fidelpost.com በዘገባው ጋዜጠኛውን ጨምሮ ሌላ የድርጅቱ የድህረገፅ ክፍል ሀላፊ ዛሬ ከሰአት ፓሊስ ጣቢያ ለምርመራ አቅንተው እነደነበር ገልጿል።

ምንጭ፦ ፊደል ፖስት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia