የነዳጅ ስለፍ...

የነዳጅ ሰልፍ ምን ባህር ዳር እና ሀዋሳ ከተሞች ብቻ እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥም አለ፤ ስራ አቁመን ለነዳጅ የምንሰለፍበት ቀን ብዙ ነው ሲሉ የቲክቫህ አ/አ ቤተሰቦች ሪፖርት አድርገዋል።

የአርባ ምንጭ፣ ዲላ ቲክቫህ ቤተሰቦችም ለነዳጅ መሰልፍ እየተደጋገመ መሆኑ አስገንዝበዋል። በዚህም በከፍተኛ ደረጃ የስራ ሰዓታቸውን እየተሻማ እንደሚገኝ አሳውቀዋል።

አንድ የባጃጅ ሹፌር የሆነ የኮምቦልቻ ቤተሰባችን ደግሞ እሱ ባለበት ከተማ ይሄ ነገር በተደጋጋሚ እንደሚከሰት ገልጿል።

'ስሜቱን አውቀዋለሁ ሰልፋ በጣም ስለሚያስጠላኝና የስራ ሰአቴን ስለሚሻማኝ ሌሊት 10:00 ሰአት እንቅልፌን አሸንፌ እነሳለሁ ነዳጅ ለመቅዳት፤ እሚገርመው ነገር ግን በዚያ ሌሊት ሄጄ እንኳን ሰልፉ እንዳለ ነው እና ይሄ ነገር መፍትሄ ቢሰጠው ባይ ነኝ' ሲል መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia