ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ምን አሉ?

- ባለፈው አንድ አመት ተኩል ትልቅ ነገሮች ባይሰራም እንደ አንድ የለውጡ መነሻ ጥሩ ጅማሬ እንደሆነ ተናግረዋል።

- በኤርትራ እና ኢትዮጵያ መካከል ላለፉት 80 ዓመታት የተለያዩ ኢትዮጵያ ላይ በነበሩ ስርዓቶች ተደጋጋሚ ጦርነትና ግጭት ሲፈጠር እንደነበር ጠቅሰው መነሻው ምንድነው በሚለው ላይ ደግሞ የውጭ ኃይሎች በአካባቢው ሰላም እንዳይኖር፣ ሁለቱ ሀገሮች ተስማምተው እንዳይኖሩ እንቅፋት በመፍጠር ከተለያዩ ስርዓቶች ጋር ስምምነት በማድረግ ጉዳዩን እዚህ ደረጃ ላይ አድርሰውታል ብለዋል።

- ላለፉት 20 ዓመታት በኤርትራ እና ኢትዮጵያ መካከል የተፈጠረው የድንበር ግጭት ዋነኛ መነሻው ከውጭ ኃይሎችና በ20 ዓመቱ ወቅት ስልጣን ላይ የነበረው በህወሓት የተፈጠረ ችግር ነው።

- በአንድ ዓመት ተኩል ውስጥ የተጀመረውን የሰላም ግንኙነት ለመቀልበስ አሁንም በየጊዜው የተለያዩ ችግሮች እየተፈጠሩ፤ የተለያዩ አዳዲስ ምክንያቶች እየተፈጠሩ ግንኙነቱን ለማደናቀፍ እየተሞከረ እንደሆነ ነው የጠቀሱት።

- በፕሬዘዳንቱ አገላለፅ ላለፉት 27 ዓመታት ኢትዮጵያን ይመራ የነበረው የህወሓት መንግስት አሁንም ድረስ ዶ/ር አብይ ስልጣን ከተረከቡበት ሰዓት ጀምረው በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል በአልጀርሱ ስምምነት መሰረት ድንበሩ እንደሚሰመርና ሰላምም መተግበር እንዳለበት ቃል ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ የህወሓት ድርጅት ይህንን ለማደናቀፍ እየሰራ መሆኑን በመጥቀስ በኢትዮጵያና በኤርትራ የተጀመረውን ሰላም ወደ ሌላ ደረጃ እንዳይቀጥል እንደትልቅ እንቅፋት እንደሆነ ነው የገለፁት።

More https://telegra.ph/TIKVAH-02-08

[VOICE OF AMERICA]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia