ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቡሌ ሆራ...

ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እና ከኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር ውይይት ያደረጉ የህብረተሰብ ክፍሎች የውሃና መንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄዎች አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም ተከታዩን ብለዋል፦

- መንግስት በጀመረው የብልጽግና ጉዞ የዜጎችን ጥያቄ መፍታት ላይ ትኩረት አድርጎ ይሰራል።

- በተያዘው ዓመት አገሪቱ በአጠቃላይ 50 ቢሊዮን ብር ለመንገድ መሰረተ ልማት በጀት ይዛለች። ከዚህ ውስጥም 2 ቢሊዮን ብር የሚሆነው በቡሌሆራና አካባቢው ለሚገነቡ መንገዶች የሚውል ነው።

- የኦሮሚያ ክልል መንግስት ከሚመለከተው ሚኒስትር መስሪያ ቤት ጋር ተቀናጅቶ የተነሳውን የውሃ ችግር ለመፍታት እንዲሰራም ጠቅላይ ሚኒስትሩ መመሪያ ሰጥተዋል።

- የአካበቢው ማህበረሰብ ብሎም የኦሮሞ ህዝብ ሌብነትን በመታገል እንዲሁም አንድነቱንና ሰላሙን በመጠበቅ ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia