#Election2012

ሳልሳይ ወያነ ትግራይ...

- ሳወት “የትግራይ ጥቅም መሰረቱ ትግራይ ባደረገው ሁለንተናዊ ትግል ይረጋገጣል” በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የመጀመርያ ጉባኤውን አካሂዷል።

- በጉባኤው የተለያዩ የሕብረተሰ ክፍሎች፣ የፓርቲ ተወካዮች በተለይም ትግራይ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች፣ የምርጫ ቦርድ ፅ/ቤት ተወካይ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የሞያ ማህበራት፣ የዩኒቨርሲቲ ተወካዮች ተገኝተው ነበር፡፡

- ጉባኤው ታህሳስ 25/2012 ዓ/ም ከሰአት በኋላ 3 ፕሬዚድየም አባላትን በመምረት በ7 ቡድን በመቧደን ሰፊ ውይይትና ክርክር በማድረግ የፓርቲው ፕሮግራም አፅድቋል፡፡ ታህሳስ በ26/2012ዓም ከሰአት በኋላ የፓርቲው ብሄራዊ አመራር (ማእከላዊ ኮሚቴ) መርጧል።

- በ3 የምርጫ አስፈፃሚዎች እየተመራ 2 ሴቶች ን ያካታተ 25 ብሄራዊ አማራር፤ 1 ሴት የተካታተችበት 5 የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት መርጧል።

- ማእከላዊ ኮሚቴው ድርጅቱ በሰጠው ስልጣን መሰረት የፓርቲው ሊቀ-መንበር አቶ ሃያሉ ጎዶፋይ እና ምክትል ሊቀመንበር ደግሞ አቶ አሉላ ሃይሉን የመረጠ ሲሆን የተለያዩ ተጨማሪ ሃለፊዎችንም በየዘርፉ ሰይሟል።

(አውሎ ሚዲያ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia