ጠቅላይ ሚኒስትሩ በያቤሎ...

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በኦሮሚያ ክልል በምትገኘው የቦረና ዞን ከያቤሎ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ውይይት አካሄዱ። በንግግራቸውም ወቅት የከተማዋ ነዋሪዎች የፍቅርና ሰላም እሴቶችን በአንድነት አጽንተው፣ ለኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልማት መሠረት እንዲያደርጓቸው አሳስበዋል።

የማኅበረሰቡ ሽማግሌዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት የታዩትን የሃይማኖትና ሌሎች ነጻነቶች ዋቢ አድርገው፣ ኢትዮጵያ እየተጓዘችበት የምትገኘውን የዴሞክራሲ ጎዳና አድንቀዋል። በተጨማሪም፣ የአካባቢውን የመሠረተ ልማት፣ የውኃ እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፍላጎት እንዲሁም የአርብቶ አደሩን ማኅበረሰብ ፍላጎት ከማሟላት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንሥተዋል።

#PMOEthiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia