ፕሬዝዳንት ትራምፕ በትዊተር ገጻቸው...

- ኢራን በ ጄነራሉ ግድያ አጸፋ ለመስጠት "የአሜሪካ ንብረቶች ላይ ማነጣጠሯን በድፍረት እየተናገረች ትገኛለች" ብለዋል።

- አሜሪካ 52 የኢራን ተቋማት ላይ ማነጣጠሯን በመግለጽ ኢራን ጥቃት ከፈጸመች "አንዳንዶቹ ለኢራንና ለኢራናውያን ባሕል ትልቅ ቦታ ያላቸው ናቸው፤ በፍጥነትና በማያዳግም ሁኔታ ነው ምላሽ የምንሰጠው" ብለዋል። "አሜሪካ ሌላ ማስፈራሪያ አትፈልግም" ሲሉም አክለዋል።

- ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራን 52 ስፍራዎች የተመረጡት በአውሮፓውያኑ 1979 በኢራን በሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ ታግተው የነበሩትን 52 አሜሪካውያንን ለማስታወስ መሆኑን ገልፀዋል። እነዚህ የኢምባሲው ሠራተኞች ለአንድ አመት ያህል ታግተው ቆይተው ነበር።

- ፕሬዝዳንት ትራምፕ ይህንን የትውተር መልዕክታቸውን ባሰፈሩ በጥቂት ደቂቃ ውስጥ የአሜሪካ መንግስት ተቋም የሆነ አንድ ድረገጽን "የኢራን ሳይበር ሰኪዩሪቲ ግሩፕ ሀከር" የተሰኘ የኮምፒዩተር ጠላፊ ቡድን እንዳይሰራ አድርጎታል።

(BBC)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia