ታላቅ አለም አቀፍ የዳዕዋ ዝግጅት በቡታጀራ ከተማ!

ከ 1 መቶ ሺህ በላይ ኢትዮጵያዋንም ጨምሮ የአለም ሀገራት የእስልምና እምነት ተከታዮችን እንግዶች ተቀብላ እያስተናገደች ነዉ። "አበሻ እጅቲማዕ" በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

ይህ በሀገራችን ለመጀመርያ ጊዜ የሚካሄደዉን ታላቅ አለም አቀፍ የዳዕዋ ዝግጅት ነዉ። ከህንድ ፣ከሱዳን ፣ከኬንያና ከሌሎች የአለም ሀገራት የተዉጣጡ የእስልምና እምነት ተከታዮች የዳዕዋዉ ተሳታፊ ናቸዉ።

ከ1 መቶ ሺህ በላይ አትዮጵያዉያን ጨምሮ የአለም ሀገራት እያስተናገደች ትገኛለች። "አበሻ እሽቲማ" ዳዕዋ ከሕዳር 26 ቀን 2012 ዓ.ም ለተከታታይ ሶስት ቀናት ማለት እስከ እሁዱ የሚቀጥል ነዉ፡፡

የከማዉ ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸዉን ለእንግዶች ክፍት አድርገዉ እንግዳ የመቀበል ባህላቸዉን በከፍተኛ ሁኔታ እያንጸባረቁ ነዉ። ከተለያዩ የአለም ሃገራት ማለትም ከአፍሪካና ከአውሮፓ ሃገሮች ከ አንድ መቶ ሺህ በላይ የእስልምና የእምነቱ ተከታዮች የዳዕዋዉ ተሳታፊዎች ናቸዉ።

(Gurage Zone Administration Public Relation Office)

#SRTA

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia