#LemmaMegersa #PP

"...አይሆንም ያልኩበት ምክንያት አንደኛ እኛ የኦሮሞ አመራር አባላት የኦሮሞ ህዝብ አምኖን ያቀረበልን ትላልቅ ጥያቄዎች አሉ፤ እነዚህ ጥያቄዎችን እንመልስላችኃለን ብለን ቃል ገብተናል። ህዝባችን ይህን ጥያቄ ያቀረበልን የትላንቱን #ኦህዴድ ስም ለውጠንለት #ኦዴፓ ካልን በኃላ ነው። ስለዚህ ህዝቡ ጥያቄውን አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት ብሎ የሰጠው ለሀገራዊ ፓርቲ ሳይሆን ለኦዴፓ ነው። ስለዚህ የህዝቡን ጥያቄ ሳንመልስ ይህን ማድረግ ትክክል አይደለም፤ እምነት ማጉደል ይሆናል እናም ጥያቄዎቹን ቆጥሮ እንደሰጠን መመለስ አለብን የሚል እምነት አለኝ።" አቶ ለማ መገርሳ

.
.
"...የመደመር ፍልስፍና የምንለው ለውጡ የሚመራበት ፍኖተ ካርታ፤ እይታ ነው። በበፊቱ አግባብ መሄድ አንችልም። ጠንካራ ጎኖችን ከድሮ እናስቀጥላለን። ደካማ ጎኖችን ማረም አለብን። ይሄ ለውጡ በምን አይነት ፍኖተ ካርታ ይመራ የሚል የህዝብም የሊሂቃንም ጥያቄ ነበር። በምንድነው የምንመራው ? ፍኖተ ካርታ የለም የሚል አንድ አመት፣ አንድ አመት ተኩል ይሆናል ለውጡ ከተጀመረ በኃላ፤ የመደመር ዋነኛው አስፈላጊነት ለውጡ በምን ጎዳና ይመራል? ከዴሞክራሲ አኳያ እንዴት ነው የምንመራው? ከሰላም አኳያ እንዴት ነው የምንመራው? ከኢኮኖሚ አኳያ እንዴት ነው የምንመራው? ከፖለቲካ አኳያ ቀጣይ እይታችን፣ ቀጣይ ሃሳባችን ፍኖተ ካርታው ባጠቃላይ ሚመራበት ምንድነው የሚለውን ሚመልስ ነው።" አቶ ፍቃዱ ተሰማ (የብልፅግና ፓርቲ ኦሮሚያ ፅ/ቤት ኃላፊ)

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot