#ADAMA

የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ (ቪኦኤ) የአፋን ኦሮሞ ክፍል ሪፖርተር የሆነው ጋዜጠኛ ሙክታር ጀማል በአዳማ ከተማ 'ጀማል መጋዘን' ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በመንገድ ላይ ቃለ-መጠይቅ እያደረገ ሳለ ድብደባ እና ዘረፋ ተፈጽሞበታል። ጭንቅላቱ እና ወገቡ ላይ ጉዳት ያጋጠመው ጋዜጠኛ ሙክታር ሆስፒታል ተኝቶ የህክምና አገልግሎት እየተከታተለ ነው። ሙክታር ቃለ-መጠይቅ እያደረገ ሳለ የተደራጁ ወጣቶች መጥተው ድብደባ እንደፈጸሙበት ያስረዳ ሲሆን፤ "ቦርሳዬን ሲበረብሩ የኢቮኤ መታወቂያ ካርድ ካዩ በኋላ ትተውኝ ሄዱ" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።

Via ቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia