#PMOEthiopia

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ያገኙት የኖቤል የሰላም ሽልማት ለሰላም የተሰጠ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታወቀ። ፅህፈት ቤቱ ባወጣው መግለጫ ይህ ለሰላም የተሰጠ ሽልማት በመሆኑም መላው ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ለሰላም እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል።

የዘንድሮው የኖቤል የሰላም ሽልማትም የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል መሆኑንም አስታውቋል። ኢትዮጵያን አዲሲቷ የተስፋ አድማስ በማድረግ የበለፀገች እንድትሆን የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የማንቂያ ጥሪ መሆኑንም ነው ያመለከተው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የ2019 የኖቤል የሰላም ተሸላሚ በመሆን በዘርፉ 100ኛው ተሸላሚ ሆነዋል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia