#HERQA

የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ኤጀንሲ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተለያዩ መስፈርቶችን ሳያሟሉ ተምረው ያስመረቋቸውና በመማር ላይ ያሉ ተማሪዎችን በተመለከተ መንግስት ውሳኔ እንዲሰጥበት ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ማቅረቡን አስታወቀ።

በኤጀንሲ የዕውቅና አሰጣጥ ዳይሬክተር አቶ አብይ ደባይ፤ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተለያዩ መስፈርቶችን ሳያሟሉ አስተምረው ያስመረቋቸውና በማስተማር ላይ የሚገኙት ተማሪዎች ቁጥር በርካታ ነው። የተማሪዎችን መረጃ ለመደበቅ ሁለት ሬጅስትራር ያሏቸው፤ ግብር እንዳይከፍሉ የተለያዩ መረጃዎችን የሚያቀርቡ ተቋማት እንዳሉ ተገንዝበናል።

ተቋማቱ አስተምረው ያስመረቋቸውና ተጠያቂነትን በመሸሽ ለኤጀንሲው ያላቀረ ቧቸው ሊኖሩ ስለሚችሉ ችግሩ የሰፋና ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ በመሆኑ ከፍተኛ አመራሩ ውሳኔ እንዲያሳልፍ ቀርቧል::

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia