#ሰበታ

በህገ ወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ ሊገቡ የነበሩ በርካታ የጦር መሳሪያዎች በሰበታ ከተማ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነግሯል። የሰበታ ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፥ የጦር መሳሪያዎቹ ኮድ 3 አ.አ በሆነ ተሽከርካሪ ውስጥ ተደብቀው ወደ አዲስ አበባ በመጓጓዝ ላይ እያሉ ነው በቁጠጥር ስር የዋሉት። ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎቹም የፀጥታ አስከባሪ አካላት ባደረጉት ክትትል እና ፍተሻ በቁጥጥር ስር ሉውሉ መቻላቸውም ነው የተገለፀው።

የሰበታ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ እንዳስታወቀው፥ በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር የዋሉት ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች 40 ክላሽንኮቮች ናቸው። በአሁኑ ወቅት የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ አካላት እንዳሉ በመግለፅ ህብረሰተቡ አጠራጣሪ ነገሮችን በሚመለከትበት ጊዜ ለፀጥታ አካላት እንዲያሳውቅም ጥሪ አቅርቧል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia