የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል፡፡ ሠልፉ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በምዕመኗቹ ላይ የሚፈፀመው ግፍ እንዲቆም የሚጠይቅ ነው፡፡ በሰልፉ ላይ ‹‹በቤተ ክርስቲያንና በምዕመኖቿ ላይ የሚፈጸመው ግፍና መከራ ይቁም፡፡ በቤተ ክርስቲያንና ምዕመኖቿ ላይ ግፍ የፈጸሙት በሕግ ይጠየቁ፡፡›› የሚሉ መልዕክቶች ተላልፈዋል።

ሰልፍ ከተካሄደባቸውን ከተሞችና አካባቢዎች መካከል ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ይገስኙበታል፦

•ራያ ቆቦ
•ኮን
•ዳንግላ
•ሞጣ
•ዳባት
•ጫጫ
•መሐል ሜዳ
•ውጫሌ
•ደላንታ ወረዳ
•ደብረ ብርሃን
•ደብረ ማርቆስ
•ወልዲያ
•ባህር ዳር
•ላልይበላ
•ደባርቅ
•ቡሬ
•ቢቸና
•ፍኖተ ሰላም
•ወረኢሉ
•ኢንጂባራ
•መርዓዊ
•አረሪቲ

በበርካታ ቦታዎች የተካሄዱት ሰልፎችም በሰላም መጠናቀቃቸውን የቤተሰቦቻችን አባላት ገልፀዋል።

#TIKVAH_ETH

ፎቶ: ከማህበራዊ ሚዲያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia