#ADDISABEBA

‘የአልሸባብ አባል’ በ10 ቦታዎች የሽብር ጥቃት ሊፈፅሙ ነበር በሚል ተከሰሱ!

•የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አዲስ አበባ ስቴዲየም ከኢላማዎቹ መካከል ነበሩ ተብሏል

ከስድስት ወራት በፊት በብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት ክትትል #የአልቃይዳ የምስራቅ አፍሪቃ ክንፍ ብሎ ራሱን የሚጠራውን የአልሸባብን ዓላማ ለማሳካት በአዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ 10 ቦታዎች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ዝግጀት ሲያደርጉ ነበር የተባሉት አዲሃመን አብዶ ክስ ተመሰረተባቸው።

ግለሰቡ በኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ እና ኢትዮጵያ ላይ በተመሳሳይ ወቅት በተነጣጠሩ ጥቃቶች ላይ የአዲስ አበባ ጥቃት ለማቀናጀት የቦታ መረጣ እንዲያከናውኑ ተመልምለው ነበር ሲል ዓቃቤ ህግ ክሱን መስርቷል። ግለሰቡ ከትላልቅ ህንጻዎች ላይ በመሆን የቦሌ አየር መንገድ ማረፊያን በምስል አስቀርተዋል ሲል ያተተው ክሱ ሀያት ሬጀንሲ፣ ስካይ ላይት ሆቴል፣ በመገንባት ላይ ያለውን የንግድ ባንክ ህንፃ አና ሌሎችም ሰዎች በብዛት የሚሰበሰቡባቸውን ቦታዎች በምስል አስቀርተዋልም ብሏል።

ሁለተኛ ተከሳሽም ለዋና ወንጀል አድራጊ ሀሰተኛ ሰነዶችን በማዘጋጀት በሽብር አዋጁ መሰረት የሽብር ወንጀልን በመርዳት ተጠርጥረው ክስ ተመስርቶባቸዋል። ለዋና ወንጀል አድራጊ የትምህርት ማስረጃ ሰነዶችን በጅግጅጋ ከተማ ተምረው እንዳጠናቀቁ በማስመሰል አዘጋጅተዋል፤ በዚህም ሊፈፀም ለታቀደው ወንጀል እገዛ አድርገዋል ሲል ዐቃቤ ህግ በአባሪነት ከሷቸዋል።

የሶማሊያ ዜግነት ያላቸው አንደኛ ተከሳሽ የጅቡቲን ሕገወጥ የጉዞ ሰነድ ፓስፖርት ይዘው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ወደ ቱርክ ለመብረር ቪዛ በማግኘት በቀጣይ እቅድ እንደነበራቸው ለማወቅ ተችሏል።

https://telegra.ph/E-09-16

ምንጭ፦#አዲስ_ማለዳ_ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia