እድሜዋ ትንሽ ሀሳቧ ትልቅ---ሰላም⬆️

ሀዋሳ ከተማ ኦሲስ ሆቴል አጥገብ ፌደራል አጥሩ ስር ቡና የምታፈላና ጎን ለጎን መጽሀፎችን ለሚያነቡ #በነጻ እንዲጠቀሙ መልካም የንባብ ባህልን አስተዎጽኦ የምታደርግ ሰላም የምትባል ልጅ አለች። በዚህ ብቻ አላበቃችም ለጎዳና ልጆች እዛው አካባቢ ዘንቢልና የተለያዩ ማጌጭዎችን በመያዝ በቀላሉ እንዲሰሩ እያደረገች ትገኛለች።

አሁንም ቡናዎን እየሸጠች ባዶ ካርቶን አስቀምጣ (1ደብተር፣ 1 እስክሪብቶ፣ 1 እርሳስ፣ ለእኛ ብዙ ነው) የሚል ጽፋ ካርቶን ላይ በ4 አቅጣጫ ለጠፈችበት ሰው አልተጠራጠራትም ካርቶን ላይ የቡና መልስ ወይም ከኪስ በማውጣትና፣ ማቴሪያሉን ገዝተው በማምጣት፣ ትላንት ለፍሬ በቅቶ ብዙ ልጆችና እናቶቻቸው ጭምር በመገኘት ተረክበዎል። ለ1 ሰው ከ6 ያላነሰ እስክርቢቶና እርሳስና ደብተር ተከፉፋሏል።

ለታሰበው አላማ ከጎኗ የነበሩ ልጆችም ቲሸርት አሳትመው ለብሰው ደብተሮቹን በመቁጠርና በማስተካከል ተወጥረው ነበር። ብራቮ ሰላም ቡና በሏት "ግን ትንሽ ልጅ ነች ሀሳቧ ትልቅ ነው" ምስጋና ይገባታል።

Yared Tassew/TIKVAH-ETH/

@tsegabwolde @tikvahethiopia