“በጸጥታ ኀይሎች ሕይወቱ ስላለፈው ሙሉጌታ ፖሊስ #መረጃ አልሰጠንም” ቤተሰቦች

•ፖሊስ በጉዳዩ ላይ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል

ሰኔ 18/2011 ጠዋት 4 ሰዓት አካበቢ በተለምዶ ሳሪስ አዲስ ሰፈር ድልድይ አካበቢ በሚባለው ልዩ ቦታ በፀጥታ ኀይሎች ሕይወታቸው አልፏል የተባሉትን የሙሉጌታ ደጀኔን ግድያ በተመለከተ መረጃ እያገኙ እንዳልሆነ ቤተሰቦቻቸው ቅሬታ አቀረቡ።

በዕለቱ ኹለት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት አድርሰው በመመለስ ላይ ሳሉ ሲቪል የለበሱ የጸጥታ ኀይሎች በመኪና እንደተከተሏቸውና እሳቸውም ለመሸሽ መሞከራቸውን የሟች ታናሽ ወንድም ዮናስ ደጀኔ ተናግረዋል።

በዕለቱ ሟች ሙሉጌታ እኚህ ማንነታቸውን ያላወቋቸው ኹለት ሰዎች በመኪና ሲከታተሏቸው እንደነበር እና መንገዱ በመዘጋቱም በእግራቸው ወርደው ሊሸሹአቸው ሞክረው እንደነበር ዮናስ ተናግረዋል። “ኮሮላ መኪናውን አቁሞ ነበር። እነሱም ለኹለት ይዘውታል፤ አጥፍቶ ከሆነ እንኳን ለሕግ ማቅረብ ነው እንጂ እርሱን መግደላቸው አሳዛኝ ነው” ሲሉ ተናግረዋል። “የፖሊስ ልብስ የለበሱትን ግለሰቦች እናንተ ውሰዱኝ እነሱን አላውቃቸውም በማለት ደጋግሞ ሲጠይቅ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ነግረውኛል።”

#አዲስማለዳ

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-14-2