አቶ ሙስጠፌ ተሸለሙ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን #በዛሬው ዕለት ለሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ መሐመድና ለባልደረቦቻቸው ሽልማት አበርክታለች።

ዛሬ በጅግጅጋ በተካሄደው የኦሮሞና የሶማሌ የህዝብ ለህዝብ መድረክ ላይ የተገኙት የቤተክርስቲያኗ አባቶች ለአቶ ሙስጠፋና ለባልደረቦቻቸው የቤተክርስቲያኗን የክብር ካባ ሸልመዋቸዋል።

ቤተክርስቲያኗ ለአቶ ሙስጠፋና ለባልደረቦቻቸው ሽልማቱን ያበረከተችው በተለይ አዲሱ የክልሉ አስተዳደር ለሰላም ላላው ቁርጠኝነት እውቅና ለመስጠት እንደሆነ በቤተክርስቲያኗ የሶማሌ ክልል ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ መቃሪዎስ ገልጸዋል።

ባለፈው ዓመት በጂግጂጋና አካባቢው በተነሳው ረብሻ በርካታ አብያተ ክርስቲያንና የሃይማኖት አባቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia