ናሳ አዳዲስ ፕላኔቶችን ማግኘቱን ይፋ አደረገ!

የአሜሪካው የጠፈር ሳይንስ ምርምር "ናሳ" በሥርዓተ ፀሐይ ውስጥ ከሚገኙ ፕላኔቶች ጋር ፍፁም የማይመሳሰል ፕላኔትን ጨምሮ ሦስት አዳዲስ ፕላኔቶችን ማግኘቱን ይፋ አደረገ። እነዚህ ሦስቱ ምሥጢራዊ ፕላኔቶች TOI-270 የተሰኘ ስርዓት አካል ሲሆኑ፣ በባህርያቸውም እንደ ማርስ እና እንደ ምድር ድንጋያማ እንዲሁም እንደ ሳተርን እና እንደ ጁፒተር ጋዛማ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ የፕላኔቶቹ መገኘት አዳዲስ ዓለማትን ለማግኘት ለሚጥሩ ተመራማሪዎች መልካም ዕድል ሊሆን እንደሚችል ሳይንቲስቶች ጠቁመዋል። በአዳዲሶቹ ፕላኔቶች ህይወት ያላቸው አካላት ሊኖርባቸው እንደማይችሉም ተገምቷል።

ምንጭ፦ ኢንዲፔንደንት/#etv/
@tsegabwolde @tikvahethiopia