ከላይ ያለውን የድምፅ ፋይል ይክፈቱት🔝

የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ ዘገባ~የሲዳማ ዞን ከተሞች!

የሲዳማን ክልል እንሁን ጥያቄ ተከትሎ በዞኑ ከተሞች የተቀሰቀሰው ሁከት ዛሬም ቀጥሎ ውሏል፡፡ በሁከቱ እስከ አሁን የዘጠኝ ሰው ህይወት አልፋል፤ በርካቶች ቆስለዋል፤ ግምቱ ያልታወቀ ንብረት ወድሟል፡፡ የሁከቱ ሰለባ የሆኑ እንደሚናገሩት በአንዳንድ በሲዳማ ዞን ከተሞች ተቃውሞው ዛሬ መልኩን ቀይሮ ማንነትን በመለየት፣ የመኖሪያ ቤትና ንብረት ላይ ጥቃት ደርሷል፡፡ መንግሥት ተጨማሪ ኃይል በማስገባት ሰላማችንና ደኅንነታችንን ያረጋግጥ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ትናንት በሀዋሳ ከተማ ሦስት ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል፣ ዛሬ ሀዋሳ #የተረጋጋች መሆኑ ታውቋል፡፡

በሌላ በኩል ሲአን ዛሬ በሰጠው መግለጫ ከአስር በላይ ሰዎች በመልጋ ወረዳና አካቢው ሞተዋል ብለዋል፡፡ በግጭቱ ማዘናቸውን የገለፁት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ህዝቡ #እንዲረጋጋ ጠይቀዋል፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ ችግሩን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የፀጥታ ኃይል እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡

Via #VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia