#UpdateSport ትናንት ምሽት #በሉዛን በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ ውድድር በወንዶች 5 ሺህ ሜትር አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ አሸንፏል። ዮሚፍ ርቀቱን በ13 ደቂቃ ከ56 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት አሸናፊ ሆኗል።አትሌት ሰለሞን ባረጋ ደግሞ 13 ደቂቃ ከ1 ሰከንድ ከ99 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ውድድሩን 2ኛ በመሆን አጠናቋል። አትሌት ጥላሁን ሃይሌ 13 ደቂቃ ከ3 ሰከንድ ከ9 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 3ኛ ደረጃን ይዟል።በወንዶች 1 ሺህ 500 ሜትር ደግሞ አትሌት አያንለህ ሱሌይማን 3 ደቂቃ ከ30 ሰከንድ ከ79 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ውድደሩን በሶስተኝነት ጨርሷል።

Via #fbc
🗞ቀን ሰኔ 29/2011 ዓ/ም
@tikvahethsport