#update የኦሮሚያ ክልል የሰላምና የልማት ኮንፍረንስ ከነገ ጀምሮ እንደሚካሄድ ተገለፀ። የሰላምና የልማት ኮንፍረንስ ከነገ ጀምሮ በሁሉም የኦሮሚያ ክልል ዞኖች፣ የከተማ አስተዳድሮች እና ወረዳዎች የሚካሄድ መሆኑም ተገልጿል።

በኮንፍረንሱም በኦሮሚያ ክልል ሰላምን ስለማስፈን እና በክልሉ የህግ የበላይነትን ማስከበር የሚሉ ጉዳዮች ላይ እንደሚመከር የኦዲፒ ማእከላዊ ጽህፈት ሀላፊ አቶ አዲሱ አረጋ አስታውቀዋል።

እንዲሁም የክልሉን ህዝብ ከልማት ተጠቃሚ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ እንደሚመከርም ገልፀዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የተጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል፣ ያጋጠሙ ችግሮችን በመቅረፍ በአንድነት በመሆን የጋራ አቋም መያዝ ላይ ውይይት እንደሚደረግም አስገንዝበዋል።

Via #fbc
🗞ቀን ሰኔ 27/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia