#update የጣና ሐይቅን እምቦጭ ለመከላከል አዲስ የመረጃ ቋት ሥርዓት ዛሬ ይፋ ተደርጓል፡፡ የመረጃ ሥርዓቱን የቀረጸው ዐለም ዐቀፍ የጣና መልሶ ማቋቋም ማኅበር ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ነው፡፡ ማኅበሩ ከአየር ጠቃሚ መረጃዎችን የሚሰበስብ ሰው አልባ በራሪ ካሜራም ወደ ሀገር ማስገባቱን የአማራ መገናኛ ብዙኻን ዘግቧል፡፡ ሥርዓቱ ስለ እምቦጭ አረም የሚቀርቡትን የተለያዩ መረጃዎችና አሃዞችን ፈትሾ መፍትሄዎችን የጠቆመ ሲሆን ዐለም ስለ ጣና ከሚሰበሰበው የመረጃ ቋት በቀጥታ በኢንተርኔት መረጃ እንዲያገኝ ያስችላል- ብለዋል የማኅበሩ ሊቀመንበር ዶክተር ሰለሞን ክብረት፡፡ ለመረጃ ቋቱም በቅርቡ ድረ ገጽ ይዘጋጅለታል፡፡

Via AMMA/wazema/
🗞ቀን 14/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia