#update የ10ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተናን የጥያቄዎች መልስ #በቴሌግራም ለመቀባበል የሞከሩ ተማሪዎች መያዛቸው ተሰምቷል። ትምህርት ሚኒስቴር በዘንድሮው የ10ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና አንዳንድ ተማሪዎች በቴሌግራም ማህበራዊ ድረ ገፅ ተጠቅመው ያልተገባ ማድረጋቸውን ለሸገር ራድዮ ተናግሯል።

ሸገር ራድዮ 102.1 በዚህ በብሔራዊ ፈተና ወቅት እንዴት ተማሪዎች #የእጅ_ስልክ የመሳሰሉ መሳሪያዎችን ይዘው ወደ ተማሪ ቤት ዘለቁ ቁጥጥርስ ምን መሳይ ነበር ብሎ ጠይቋል። ትምህርት ሚንስቴር ስለጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ተናግሯል። ትናንት የጀመረው የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እስከ ሰኔ 5፣2011 ዓ.ም እንደሚስጥ ታውቋል።

ዘንድሮ 1,277,533 የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች የመልቀቂያ ፈተናቸውን ለመውሰድ በተማሪ ቤታቸው ወንበር ላይ እንደሚቀመጡ የአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ መናገሩን ሰምተናል።

ምንጭ፦ ሸገር ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia