#update በህንድ በምትተዳደረው ካሽሚር ግዛት ውስጥ የስምንት አመት ልጅ ደፍረው፣ አሰቃይተው የገደሏት ሶስት ግለሰቦች የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ መረጃ አደባብሰው አጥፍተዋል የተባሉ ሶስት ፖሊሶች በአምስት አመት እስር እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ከአርብቶ አደር ቤተሰብ የተወለደችው ህፃኗ ካቱዋ ከተማ አካባቢ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ተገድላ የተገኘችው ባለፈው አመት ነበር። የልጅቷ መገደል በከፍተኛ ሁኔታ የሚዲያ ሽፋን ያገኘው የሂንዱ ቀኝ ክንፍ አክራሪዎች በወንጀሉ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን እስር ተቃውመው ሰልፍ በማድረጋቸው ነበር።

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia