#update የኢትዮጵያ የብሄራዊ የእርቅ ኮሚሽን አባላት ከሰኔ 3-7 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ናይሮቢ ገብቷል።

ቡድኑ በናይሮቢ ቆይታው በኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ የተካሄዱ የሃቅ እና እርቅ አፈላላጊ ኮምሽን እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ትምህርት ለመቅሰም የሚያስችል የልምድ ልውውጥ ያደርጋል።

ከዚህም በተጨማሪ በኬንያ የብሄራዊ የአንድነት ኮምሽን አስራር፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ለሰላም ግንባታ በሚኖራቸው ሚና ላይ ስልጠና ይወስዳሉ።

ጉብኝቱን በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና መቀመጫውን እንግሊዝ ያደረገ በሰላም ግንባታ ላይ የተሰማራ Conciliation Resources የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ያዘጋጁት ነው።

Via የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia