#update የጋሞ እና ኮሬ የህዝብ ለህዝብ ትስስር መደረክ በአርባምንጭ ከተማ ተካሄደ። የጋሞ ዞን ዋናአስ ተዳዳሪ አቶ አርኮ ደምሴ በጋሞእና ኮሬ ሕዝብ መካከል ለዘመናት የነበረውን ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ለማሻገር ታስቦ የሁለቱ ብሔረሰቦች የህዝብ ለሕዝብ ትሰስር መድረክ መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡

የጋሞ ከፍተኛ ዳጋማ አካባቢዎች የጥንታዊ ሰው መገኛ እንደሆኑ በርካታ የታሪክ መጻህፍት ይመሰክራሉ ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ከጋሞ አካባቢ ተንቀሳቅሰው በቦታ ርቀት ተለያይተው የቆዩት ሁለቱ ብሔረሰቦች አሁን የፈጠሩት ትስስር በኢትዮጵያ የመደመር መርህ ለሌሎች አካባቢዎችም እንደ ምሳሌ ሊጠቀስ የሚችል ነው ብለዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia