#update ፍርድ ቤት ዛሬ የሰኔ 16ቱ ቦንብ ጥቃት ተጠርጣሪዎቹን ጌቱ ግርማንና ሌሎች 4 ተከሳሾችን ክሳችሁን ተከላከሉ እንዳላቸው ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በፌስቡክ ገጹ አስፍሯል፡፡ ሌሎቹ በቀጥታ ወንጀል አድራጊነት የተከሰሱት ብርሃኑ ጃፋርጥላሁን ጌታቸውና ባህሩ ቶላ ናቸው፡፡ ተከሳሾች “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም” በማለት ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመገናኘት የመስቀል አደባባዩን የድጋፍ ሰልፍ ለመበተን ሲሉ ቦንብ ጥቃት አድርሰው 2 ንጹሃን ሞተዋል፤ ከ160 በላይ የሚሆኑትን ደሞ #በማቁሰል ሽብር ፈጽመዋል- ይላል ክሱ፡፡ ዐቃቤ ሕግም ምስክሮቹን ለችሎቱ አሰምቷል፤ ማስረጃዎቹንም አቅርቧል፡፡ ተከሳሾች በበኩላቸው ፖሊስ ምርመራ ያደረገው በማናውቀው መንገድ ነው፤ ያለ አስተርጓሚ #ምርመራ ተደርጎብናል ብለው ያቀረቡት አቤቱታ #ውድቅ ሆኖባቸዋል፡፡ የተከሳሾች መከላከያ ምስክሮች ሰኔ 25 ይሰማል፡፡

Via wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia