ባምላክ ጥቃት ተፈፅሞባቸው ነበር...

የግብጹ ዛማሌክ ከሞሮኮው ሬይኔሳንስ ቤርካን (RS Berkane) ያደረጉትን የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የእግር ኳስ ጨዋታ የዳኙት ባምላክ ተሰማ ሜዳ ውስጥ ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል። ባምላክ ጥቃቱ የተፈጸመባቸው ባለፈው እሁድ የተደረገውን ጨዋታ በዳኙበት ወቅት ነው። የግብፅ ሰዎች እንደሚሉት ጥቃቱን የፈጸሙት የሞሮኮ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን እና የሬይኔሳንስ ቤርካን ፕሬዝዳንት ፎክዚ ሌክጃ ናቸው። ክለቡ በደርሶ መልሱ ጨዋታ ዳኛ ባምላክ ተሰማ ፍጹም ቅጣት ምት መስጠታቸውን በመቃወም ክስ እንደሚመሰርትባቸው አስታውቋል። የግብፁ ዛማሌክ በመለያ ምት አርኤስ ቤርካን የተባለውን የሞሮኮ ክለብ አሸንፎ የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ባለቤት የሆነው ባለፈው እሁድ ነበር።

Via #Eshete_Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia