የካርታው ነገር...

የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቅዳሜ እለት በድረ ገፁ ላይ የወጣውን ካርታ ማን እንዳተመው ለማወቅ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ገለፀ።

የሚኒስትሩ ቃል አቀባይ፣ አቶ ነቢያት ጌታቸው፣ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት እንዴትና በማን ካርታው ድረ ገፃቸው ላይ እንደወጣ ይጣራል ብለዋል።

ቃል አቀባዩ አክለውም ማን እንዳተመው ከተለየ በኋላ አስፈላጊውን እርምጃ እንወስዳለን በማለት ተናግረዋል።

“ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራትም ሆነ ከሌሎች ጋር ላላት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ልዩ ትኩረት ትሰጣለች፤ ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተልነው ነው’ ብለዋል።

ሶማሊያን የኢትዮጵያ አካል እንደሆነች የሚያሳይና ለሶማሌ ላንድን እውቅና የሚሰጠው ካርታ ባለፈው ቅዳሜ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ድረ ገፅ ላይ ከታተመ ወዲህ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በርካቶች ሲቀባበሉት ነበር።

ሚኒስትር መሥሪያ ቤቱም ወዲያውኑ ካርታውን ከድረገፁ ላይ በማንሳት #ይቅርታ ጠይቋል።

Via #bbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia