ሰበር ዜና‼️

የዊኪሊክስ መስራች ጁሊያን አሳንጅ በቁጥጥር ስር ዋለ። በስዊዲን የወሲብ ጥቃት በመፈፀም ተጠርጥሮ በህግ የሚፈለገው ጁሊያን አሳንጅ ላለፉት ሰባት ዓመታት በለንደን በሚገኘው የኢኳደር ኤምባሲ ተጠልሎ ቆይቷል።

የብሪታኒያ ፖሊስ አሳንጅ በቁጥጥር ስር መዋሉን ይፋ አድርጓል። ኢኳዶር በኤምባሲው የሰጠችው ጥገኝነትን ማቋረጧን ተከትሎ ነው በቁጥጥር ስር የዋለው። ሀገሪቱ በኤምባሲዋ ያስጠለለችው አሳንጅ በተደጋጋሚ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በመጣሱ ነው ያቋረጥኩት ብላለች።

ፖሊስ የዌስት ሚኒስቴር ማጀስትሬት ፍርድ ቤት በፈረንጆቹ 2012 ባወጣበት የእስር ማዘዣ መሰረት ነው በቁጥጥር ስር ያዋለው።

Via #fbc #cnn
@tsegabwolde @tikvahethiopia