አሳዛኝ ዜና‼️

በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን ጊርኛአዶ ወረዳ በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የ13 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ የ13 ሰዎችን ህይወትን ለቀጠፈው አደጋ መንስኤም ሰራተኞችን ጭኖ ወደ ጫት ማሳ በመጓዝ ላይ የነበር የጭነት አይሱዚ በመገልበጡ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በዚሁ አደጋ አራት ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን÷ በቦና ሆስፒታል ክትትል እየተደራገላቸው ይገኛል፡፡

የሲዳማ ዞን ፓሊስ መምሪያ የትራፊክ አደጋ መቆጣጠር የስራ ሂደት ባለቤት ኢንስፔክተር ሀኃይሉ ታፈሰ እንደገለጹት÷ ተሽካርካሪውን ረዳቱ ይዞት የነበርና ከፍጥነት በላይ ሲያሸከረክር አደጋው ደርሷል፡፡ ረዳቱ መንጃ ፈቃድ እንዳልነበረውም ነው ኢንስፔክተር ሀኃይሉ የገለጹት፡፡

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia