የባልደራስ ምክር ቤት የፖለቲካ ስልጣን ጥያቄ የለውም!!

ከጋዜጠኛ #እስክንድር_ነጋ መግለጫ በፊት የባላደራ ምክር ቤቱ የአቋም መግለጫ በጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ተነቧል።

በጠ/ሚኒስትሩ ቢሮ መግለጫ እንድትሰጡ መንግስት ፈቅዶላችሁ ነበር። ለምን አልተጠቀማችሁበትም? ለጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የቀረበለት ጥያቄ ነበር።

መልስ፦

እኛ ቤተመንግስት አንገባም። የህዝብ ድምፅ ነን። ለወደፊቱም ህዝብ መሃል እንጂ ቤተመንግስትም ሆነ ሌላ የመንግስት ተቋም ውስጥ ሆነን መግለጫ አንሰጥም። በሚቀጥለው ምርጫ የመወዳደር ፍላጎት ፈፅሞ የለኝም እንደ አጠቃላይ እራሱ የባልደራስ ምክር ቤት የፖለቲካ ስልጣን ጥያቄ የለውም። ባቋራጭ ስልጣን ለመንጠቅ የሚባለው ነገር ከንቱ ውንጀላና የተነሳውን የመብት ጥያቄ ለማዳፈን የቀረበ ምክንያት ነው።

Via Nafkot Eskinder
@tsegabwolde @tikvahethiopia