#update የደቡብ ሱዳን ወታደራዊ ፍርድ ቤት ባለፈው ዓመት ሁለት ሰላማዊ ሰዎችን በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ #ገድለዋል በተባሉ 3 ወታደሮች ላይ #ሞት ሲፈርድ በአንድ ወታደር ላይ ደግሞ የ10 ዓመት እሥራት በየነ። የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው ባለፈው ዓመት የተፈጸመው የዚህ ግድያ ዓላማ #ዘረፋ ነበር። ትናንት ያስቻለው ፍርድቤቱ ከወታደሮቹ ጋር ተባብረዋል ከተባሉ ሁለት ሲብሎች አንዱ እድሜ ይፍታህ ሌላኛው ደግሞ የ8 ዓመት እሥራት ተፈርዶበታል። አራቱም ወታደሮች ማዕረጋቸው ተገፎ ከጦር ኃይሉም መሰናበታቸው ተዘግቧል።

Via ዶቼ ቨለ
@tsegabwolde @tikvahethiopia