በአዲስ አበባ የተጠራ ሰልፍ የለም‼️

በአዲስ አበባ ከተማ ነገ የሚካሄድ ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ፥ በነገው እለት በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠርቷል በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጭው መረጃ ትክክል አለመሆኑን አስታውቀዋል።

ለነገ ህጋዊ መስመርን ተከትሎ እና ባለቤትነቱን ወስዶ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጥያቄ ያቀረበ አካል #እንደሌለም አስታውቅዋል።

ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ አክለውም ብህረተሰቡ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚጠሩ ህጋዊ ባለቤትነት ከሌላቸው ሰልፎች ሊቆጠብ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

ምክንያቱም ይህንን አጋጣሚ እንደ ምቹ ሁኔታ የሚጠቀሙ ኃይሎች በኅብረተሰቡ ላይ #የሽብር ተግባራት ለመፈጸም የሚያስችል እንቅስቃሴ ስለሚኖር ከወዲሁ ይህንን ተገንዝቦ #ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

#በመዲናዋ ያለ ፈቃድ ሠልፍ የሚያካሄዱ አካላትም ኃላፊነት እንዳለባቸው በመረዳት ግን ህጋዊ አሰራሩን መከተል አለባቸው ሲሉም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ምንጭ፦ FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia