#update 9 ፐርሰንቱ የኢትዮጵያ ህዝብ እርዳታ ፈላጊ ሆኗል ተባለ። መንግስት ዛሬ በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው 8.8 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን የሰብአዊ #እርዳታ ይሻሉ ብሏል። ከፍተኛው እርዳታ ፈላጊ በኦሮሚያ ክልል (3.88 ሚልዮን) ሲሆን የሶማሌ ክልል 1.8 ሚልዮን ተረጂዎች አሉበት። በአማራ ክልል ደሞ ወደ 980,000 እርዳታ ፈላጊዎች እንዳሉ ገልጿል። ለዚህም መንግስት የ1.3 ቢልዮን ዶላር ገንዘብ #ያስፈልገኛል ብሎ ለእርዳታ ድርጅቶች እና ለጋሽ ሀገራት ጥሪ አቅርቧል። ከእርዳታ ፈላጊዎች ውስጥ 3.1 ሚልዮኑ ተፈናቃዮች ሲሆኑ ይህም በብሄር ተኮር ግጭት የተሰደዱ ናቸው ተብሏል።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሠረት(https://www.facebook.com/Elias-Meseret-517243322140049/)

@tsegabwolde @tikvahethiopia