አሳዛኝ ዜና‼️

በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ወለጋ ዞን በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለፀ።

የትራፊክ አደጋው በትናንትናው እለት የደረሰ መሆኑን ከምስራቅ ወለጋ ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

#ከነቀምቴ ከተማ ወደ #ሲቡ_ስሬ ወረዳ 22 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ጪንጊ በተባለች ከተማ አቅራቢያ በመገልበጡ ነው አደጋው የደረሰው።

በትራፊክ አደጋውም በሚኒባስ ተሽከርካሪው ተሳፍረው ሲጓዙ ከነበሩ 22 ሰዎች ውስጥ የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉ ነው የተገለፀው።

ምንጭ፦ Fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia