#update በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ አነሳሽነት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር "የወንዞች እና የወንዝ ዳርቻ አረንጓዴ መናፈሻ" ፕሮጀክት በይፋ ስራ የማስጀመር ስነ-ስርዓት ኢ/ር #ታከለ_ኡማ፣ የፌደራልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተከናውኗል፡፡

፨ በ3 ዓመታት ውስጥ የሚጠናቀቀው፣ 56 ኪ.ሜ የሚሸፍነው እና 29 ቢሊዮን ብር ውጪ ይደረግበታል ተብሎ የሚገመተው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፦

•በ29 ቢሊዮን ብር ወጭ ይከናወናል፤ በሦስት ዓመታት እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

•ከእንጦጦ ተራራ በጉለሌ በኩል አፍሪካ ህብረት እንዲሁም ከእንጦጦ በአፍንጮ በር በባንቢስ አድርጎ አቃቂ የውሃ ማጣሪያን ይሸፍናል(56 ኪሎ ሜትር)

•ድልድዮች፣ ሰው ሰራሽ ሐይቆች፣ አረንጓዴ ቦታዎች፣ የመዝናኛ ማዕከላት፣ የውኃ ትራንስፖርት እና የንግድ ማዕከላት ይገነቡበታል።

በተያያዘ መረጃ፦ በ50 ሄክታር ላይ ተግባራዊ የሚደረግ፣ 2.5 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚደረግበት እና በ1 ዓመት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ በተለምዶ ሸራተን ማስፋፊያ በሚባለው ቦታ ፓይለት ፕሮጀክት ይፋ ተደረጓል።

ምንጭ፦ ወ/ሮ መስከረም (የከንቲባው ቴክኒካል አማካሪ) ለTIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia