#update የሱማሊያ ጫት ነጋዴዎች ከኬንያ ጫት ማስገባታቸውን ትተው #የኢትዮጵያን_ጫት ለመግዛት መወሰናቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኻን ዘግበዋል፡፡ ኬንያ የሞቃዲሾው መንግሥት በቅርቡ ያወጣው ዐለም ዐቀፍ የነዳጅ ቁፋሮ ጨረታ ሉዓላዊ የባህር ግዛቴን አጠቃሏል በማለቷ ከቅዳሜ ጀምሮ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን አቋርጠዋል፡፡ ሱማሊያ ግን ውንጀላውን ታስተባብላለች፡፡ የሱማሊያዊያኑ ጫት ነጋዴዎች ኮሚቴ ከነገ ጀምሮ የኢትዮጵያን ጫት የምናስገባው ከሀገራችን ሉዓላዊነት ጎን መቆም ስላለብን ነው ብሏል፡፡ ሱማሊያ በቀን ከኬንያ የምታስገባው 50 ቶን ጫት 100 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ ይገመታል፡፡

Via wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia