ቴላቪቭ‼️

በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ። የ24 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ይሁዳ ባይድጋ ከሁለት ሳምንት በፊት ነበር በፖሊስ ተተኩሶበት #የተገደለው። #ሰልፈኞቹ የቴላቪቭ ዋና ጎዳናን #በመዝጋት እና በዋና ዋና መንገዶች በማለፍ ባካሄዱት ሰልፍ በእሥራኤል ዘረኝነትን እና ፖሊስ የሚፈጽመውን ከመጠን ያለፈ ጥቃት እና አድልዎ #ተቃውመዋል። በእስራኤል ምክር ቤት የሰብአዊ ሐብት ሎጂስቲክ አስተባባሪ አቶ ዮናታን ታከለ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያዊውን የገደለው ፖሊስ አሁንም በስራ ላይ ነው። ይህም ቤተ እስራኤላውያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። የዐአእምሮ ህመምተኛው ልጃቸው ይሁዳ ከቤቱ ስለት ይዞ ሲወጣ ፣እንዲደርስላቸው እናቱ ደውለው የነገሩት ፖሊስ ተኩሶ እንደገደለው ተዘግቧል። በእሥራኤል ጦር ውስጥ ማገልገሉ የተነገረውን የይሁዳን አሟሟት የእስራኤል የፍትህ ሚኒስቴር እያጣራሁ ነው ብሏል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia