ተማሪዎች አስተማሪያቸውን #በመግደል ተጠርጥረው ተያዙ‼️

ሦስት ተማሪዎች #ሞባይል ተወስዶብናል በሚል ሰበብ በአስተማሪያቸው ላይ ከተፈጸመ ግድያ ጋር በተያያዘ ኬንያ ውስጥ ተይዘው #ታሰሩ።

#ናኩሩ በተባለው የኬንያ ግዛት ሆፕዌል በተሰኘው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፊዚክስ መምህር የሆኑት ፒተር ኦማሪ በተማሪዎቹ ጥቃት የተፈፀመበት ባለፈው ሳምንት መጠናቀቂያ ላይ ነበር።
ተማሪዎቹ ቢያንስ አንድ ሞባይል በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይዘው በመገኘታቸው በመምህሩ ተወስዶብናል በሚል ነው ድርጊቱን እንደፈፀሙ የተነገረው።

ለሥነ ሥርዓትና የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ሲባል በኬንያ በርካታ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ሞባይል እንዳይዙ ይከለክላል።

ባለስልጣናት ለቢቢሲ እንደተናገሩት ጥቃቱ በተፈጸመበት ዕለት መምህሩ በሚያስተምሩበት ትምህርት ቤት ውስጥ የምሽት ትምህርትን #እያስተባበሩ ነበር።

የአካባቢው ምክትል አስተዳዳሪ ኤሊም ሻፊ እንደተናገሩት ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ 150 ኪሎ ሜትር ሰሜን ምዕራብ ርቃ በምትገኘው የናኩሩ ከተማ፤ መምህሩ በትምህርት ቤቱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ሲሄዱ ነው ጭቅላታቸው ላይ ተመትተው ለሞት የበቁት።

ኬንያ ውስጥ በመምህራንና በትምህርት ቤቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እየጨመሩ በመሆናቸው የሃገሪቱን ባለስልጣናት በእጅጉ እያሳሰበ ነው።

ባለፈው የፈረንጆች ዓመት በምዕራባዊ ኬንያ በምትገኘው ኪሱሙ ውስጥ አንድ መምህር ከተማሪዎቹ ጋር ጠንከር ያሉ ቃላትን ከተለዋወጠ በኋላ በተማሪዎቹ በገጀራ ተመትቶ ለሞት ተዳርጓል።

ከሁለት ዓመት በፊት ደግሞ ኪሲ በተባለ ቦታ የሚገኝ የአንድ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የአውሮፓ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድርን የቀጥታ ሥርጭት በቴሌቪዥን እንዳይከታተሉ በመከልከላቸው መኝታ ክፍላቸውን በእሳት አውድመውት ነበር።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia