#update በአገሪቱ የሚታዩትን #ግጭቶች ለማስቆም ወጣቱ በውይይት የሚያምንና በምክንያት ላይ የተመሰረተ ሥራ ሊያከናውን እንደሚገባ ተገለፀ፡፡በሃይማኖት በዓላት ላይ የሚታየውን አንድነትም ግጭቶችን ለመፍታት መጠቀም እንደሚገባም ተመልክቷል፡፡ በወልድያ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር አቶ ሻለሙ ስዩም፣ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናሩት፤ በአገሪቱ የሚታየውን ግጭት ለማስቆም ወጣቱ የተለያዩ የአገሪቱ ጉዳዮችን በመተንተን ለግጭት ሊያደርስ የቻለውን ነገር በምክንያት ላይ ተመስርቶ በመለየት ችግሮችንም በውይይት መፍታት አለበት ብለዋል።

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia